አዲስ ልደት ኢንተርናሽናልቸርች
ድረ-ገጻችንን በመጎብኘት የሚፈልጉትን መረጃ አግኝተው ከእኛ ጋር አብረው ጌታን ለማምለክ ኅብረታችንን እንደሚጎበኙ ተስፋ እናደርጋለን።
እኛ
በሁለት ቦታ ያለ አንድ ቸርች ነን
ራዕያችን
ራዕያችን የመንግስቱን ወንጌል የምታውጅና እውነተኛ የክርስቶስ ደቀመዛሙርትን የምታፈራ ቤተክርስቲያን ማየት ነው።
ተልዕኮአችን
ተልዕኮአችን የመንግስቱን ወንጌል በመንፈስ ቅዱስ ኃይል በመስበክ፤ የጽድቅ ተጽዕኖ የሚፈጥሩ የክርስቶስ ደቀመዛሙርትን በማፍራትና፤ በበጎ ሥራ እየበዛች የምትሔድ ቤተክርስቲያንን በመገንባት የእግዚአብሔርን መንግስት ማስፋፋት ነው።
አገልግሎቶች
የሚያገኙዋቸው አገልግሎቶች
በቸርቻችን የተለያዩ አገልግሎቶችን ያገኛሉ
Silver Spring MD
ሳምንታዊ አገልግሎቶች
እሁድ
የማለዳ ጸሎት: 10:00am – 11:00am
አምልኮ: 11:00am – 1:30pm
የወጣቶች አገልግሎት: 6:30pm – 9:00pm
የሳምንቱ አጋማሽ
ረብዕ: 6:30pm – 9:00pm
የሃሙስ ጸሎት: 10:00am – 2:00pm
አርብ
አዳር ጸሎት: 8:30pm – 12:30am
Springfield VA
ሳምንታዊ አገልግሎቶች
እሁድ
የማለዳ ጸሎት: 9:30am – 10:30am
አምልኮ: 10:30am – 1:00pm
የሳምንቱ አጋማሽ
ማክሰኞ: 7:00pm – 9:00pm
አርብ
አዳር ጸሎት: 7:00pm – 11:00pm
ቅዳሜ
የወጣቶች አገልግሎት: 7:00pm – 9:00pm
ስለ እኛ
ስለ ቸርቻችን
ታሪካችን
የኅብረታችን ታናሹ ጅማሬ የሚጀምረው ሴፕቴምበር 2008 በዋሽንግተን ዲሲ ነው። ከምስረታው ጥቂት ወራት ቆይታ በኃላ አድራሻችንን ወደ 1010 ሪፕሊይ መንገድ ሲልቨር ስፕሪንግ ሜሪላንድ ወደ ነበርንበት አዳራሽ ተዛውረን በዚያ ከአስር ዓመታት በላይ ቆይተናል። በ1010 ሪፕሊይ መንገድ ላይ በነበርንበት ጊዜ ቤተክርስቲያናችን በልዩ ልዩ መልኩ በአባላት ቁጥርም በአገልግሎቶችም ስብጥር ዕድገት ታሳይ ነበር። ሁሉም ባርኮት የነበረን ቢሆንም ቤተክርስቲያኗ ባሳለፈቻቸው ከፍታና ዝቅታም መካከል የእግዚአብሔርን ምህረት እና ምግቦቱንም በማይረሳ መልኩ የተካፈልንበትም ነበር።